Friday, February 5, 2016

በመንግስት ፓርላማ ውስጥ የውጭ ጉዳይ አስተዳደር ቀዋሚው ቁጥጥር ኮሜቴና የፈደራል ዋና ኦዲተር በተገኙበት ሰብስባ ላይ፣ “በእናንተ ሰበብ አገራችን እየተወረረች ናት” ተብለው የማእድን ሚኒስትር ሃላፊዎች መወቀሳቸው ለማወቅ ተችሏል።



እነዚህ  የፔትሮሊም ሚኒስተርና የተፈጥሮ ጋዝ  ስራ ሃላፊዎች  የሆኑት ባለፈው ጥሪ   18 / 2008 ዓ/ም  ከሰአት በኃላ  ወደ ፓርላማው  እንዲቀርቡና  በ2005ዓ/ም  በተደረገው  ኦዲት መሰረት ውድና  በከፊል ውድ ለሆኑት ማእድናት  በፍቃድ አሰጣጥ  ኣስተዳደር ግዥና  ቁጥጥር  ላይ አስመልክተው የታዩትን  ችግሮች  ለማስወገድ ማብራርያ  እንዲሰጡ ተጠይቀው  እንደነበሩና  በዋናነት ጉዳዩን የሚመለከታቸው ሚኒስትር ዴኤታ የሆኑት  ዶ/ር ዋቅ ጋሪ ፋሪ በሚመሩት የቡዱን ከፍተኛ አመራሮች  በፓርላማው መሰብሰብያ ኣዳራሽ በመገኘት  በተደረገው ስብሰባ ላይ በርከት ያሉ ጥያቄዎች እንደተነሱ ታውቀዋል።
 በስብሰባው ላይ ከተነሱት ጥያቄዎችም ሚኒስትሩ ለሶስት ኩባንያዎችና  ለከፍተኛ የማእድን አምራቾች በፍቃድ  አስጣጥ  ላይ ችግር  እንዳለና እንደዚሁም  በማአድን ስራ አከባቢዎች የሚካሄደው  ጥበቃ ላይም  ግንዛቤ የጎደለው  መሆኑንና።       መኪና የመንዳት  ፍቃድ የተሰጣቸው  ደግሞ የውድ ማእድን አዘዋዋሪዎችም የሚያገኙት ህጋዊ ምንጭ  አከባቢውን  የሚከታተሉ  ሚኒስተር  ስርዓት እንደሌለው በስብሰባው ተገለፀ።
    ይህን እድል ተጠቅመው  ጥያቄ ካቀረቡ አባላት መካከል   ወ/ሮ ስፍራሽ ብርሃነ አንድዋ ሲሆኑ። የስራ ሃላፊዎቹም ለጥያቄው የሚገባ መልስ  እንዳልሰጡበት  ያገኘነው መረጃ  አስረድቷል።

No comments:

Post a Comment