Wednesday, November 5, 2014

በትግራይ ክልል ደቡባዊ ምስራቅ ዞን ሃገረሰላም ከተማ ውስጥ የከተማ ውስጥ መንገድ አስፓልት ለመስራት በሚል ምክንያት። እንዲፈርሱ ወረቀት የተለጠፈባቸው ቤቶች። ህግና ስርዓት ባልተከተለ መንገድ የተወሰነ በመሆኑ። ነዋሪው ህዝብ መቃወሙ ተገለፀ፣




የትግራይ ክልል አስተዳዳሪዎች በሃገረሰላም ከተማ አስፓልት እንሰራለን በሚል ምክንያት። መፍረስ የማይገባውን ቤት በዝቅተኛ ካሳ እንዲፈርስ በመወሰናቸው የተነሳ። የከተማው ህዝብ መቃወሙን መረጃው አስረድቷል፣
    የህዝቡ የተቃውሞ መነሻ የሆነው። መፍረስ የማይገባቸው የአንዳንድ ግለሰብ መኖርያ ቤቶች። ለምን እንዲፈርሱ ተወሰነ? የተወሰነው የካሳ ክፍያ ሚዛናውነት የጎደለው ነው፤ ቤታቸው እንዲፈርስ የተወሰነባቸው ሰዎች ለምን ተለዋጭ መሬት አልተሰጣቸውም የሚሉ እንደሆኑና። በዚሁ ህዝባዊነት የጎደለው ተግባርም መላው የከተማው ነዋሪ ህዝብ እንደተቃወሞው መረጃው አክሎ አስረድቷል፣