Pages

Sunday, June 14, 2015

በትግራይ ምስራቃዊ ዞን የሚገኙ የዓረና/መድረክ ተቃዋሚ አባላት የሆኑት ዜጎች በገዢው ስርአት የፀጥታ አካላት ከቤታቸው ታፍነው እየተወሰዱ እንደሚገኙ ታወቀ።



ምንጮቻችን እንደገለፁት በትግራይ ምስራቃዊ ዞን ኢሮብ ወረዳ እንዳልጌዳ አካባቢ የሚገኙ የዓረና/መድረክ ተቃዋሚ ድርጅት አባላት የሆኑት አቶ ልኡል አድሓኖም ብስራት የተባሉት ወገን ግንቦት 17/2007ዓ/ም ጥዋት ላይ የምርጫ ውጤት ለመታዘብ ወደ ምርጫ ጣቢያው አምረተው ውጤቱን አይተው ባለመቀበላቸው የተነሳ ህዝብ የሰጠውን ድምፅ ለምን አታከብርም በማለት ሰዎችን ወደ አልተፈለገ መንገድ እንዲያመሩ ትቀሰቅሳለህ በሚል ምክንያት ግንቦት 22/2007ዓ/ም ወደ ዓዲግራት እስር ቤት ወሰደው እንዳስሯቸው ለማወቅ ተችሏል።