በምንጮቻችን መረጃ መሰረት በምእራባዊ ዞን ትግራይ ወልቃይት ወረዳ ቆራሪት
ከተማ በህዳር 10 2008 አ/ም ስርአቱ መሬታቸወን ነጥቆ ያፈናቀላቸው
ገበሬዎች መቋቋምያ እንዲውል ታስቦ በብዙ አቤቱታና ጥረት የተገኘው 37 ሺ ብር ጫቅለ ተስፋይና ፀጋይ ፍትዊ የተባሉ የኣከባቢው ኣስተዳደሪዎች ገንዘቡ እየቆረጡ
በማስቀረትና የት እንደዋለ ሳይታወቅ በማትረፍ የተወስነውን ብቻ ለማሰመስል እንዳከፋፈሉት ታወቀ።
ለተፈናቀሉ
ገበሬዎች ማቋቋምያ ተብሎ ከመጣው 37 ሺ ብር ከያንዳንዱ ተፈናቃይ
ገበሬ የተቀነሰው 10 ሺ ብር ስለምንና? ለምን? ተቀንሶ 27 ሺ ብር ብቻ
የታደለው በማለት ህዝቡ ጥያቄውን በማቅረብና ኣስቸኳይ
ምላሽም እንዲሰጠን" ኣለበለዚያ እስከ ፈደራል ድረስ በመሄድ ኣቤቱታቸና ጥያቄዎች እናቀርባለን በማለት ተቃውሞ
ማንሳታቸው ለማወቅ ተቻለ።