Pages

Wednesday, November 5, 2014

የጋሞጎፋ ዞን አስተዳዳሪዎች በመኸር ወቅት ለአካባቢው ህዝብ በተከታታይ ስብሰባ ላይ ጠምደውት እንደሚገኙ ከአካባቢው የተገኘው መረጃ አስታወቀ፣




በምንጮቻችን መረጃ መሰረት በደቡብ ክልል ጋሞጎፋ ዞን የሚኖር ህዝብ በመኸር ወቅት ምርቱን እንዳይሰበስብ የስርአቱ ካድሬዎች ነጋ ጠባ የተለያዩ ምክንያቶችን እየፈጠሩ፤ በአስገዳጅ ስብሰባ ላይ ጠምድውት እንደሚገኙና የስብሰባው አላማም ህዝቡን በማሰላቸት የደኢህዴን ኢህአዴግ አባል እንዲሆን በማድረግ በምርጫው ግዜ ድርጅቱን እንዲመርጡ ያለመ እንደሆነ ተገልፀዋል፣
     እየተካሄደ ባለው ስብሰባ ምክንያት ህዝቡ ምርቱን መሰብሰብ ተስኖት፤ በዝናብ እየተበላሸ መሆኑንና፤ ምሬቱን እየገለፀ እንደሆነ መረጃው ጨምሮ አስረድቷል፣