Thursday, December 20, 2012

በቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል ሰፋፊ በተፈጥሮ ደን የተሸፈነ መሬት በስመ ኢንቨስትመንት እየተጨፈጨፈ ነው ።

-->


በፓዌ ዞን በቻግኒ ከተማ ዙሪያ ከ 40 ሄክታር መሬት በላይ በተፈጥሮ ደን ተሸፍኖ የነበረ መሬት ቦታው ለክርቢት ፋብሪካ ማሰሪያ አስፈልጓል በሚል ምክንያት እየተመነጠረ መሆኑ ቷውቋል
ቀደም ሲል የክልሉ ባለስልጣናት ህጋዊ ካልሆኑ የውጭ ባለሃብቶች ጋር በመመሳጠር የአከባቢው ህዝብ ለዘመናት በእንክብካቤ ጠብቆ ያቆየውን በቀርቀሃ የተሸፈነ ሰፋፊ መሬት በመጨፍጨፉ ምክንያት በአከባቢው ህዝባዊ ተቃውሞ መቀስቀሱን የሚታወስ ነው ።