Tuesday, January 1, 2013

በዳሞት ወረዳና በፍኖተ ሰላም ከተማ የሚገኙ የኢህአደግ ስርዓት ታጣቂዎችን ታህሳስ 17,2005 ዓ/ም በመሰብሰብ ጥብቃ እንዲያጠናክሩ መመርያ ተሰጣቸው።

በአማራ ክልል በምዕራብ ጎጃም በዳሞት ወረዳና በፍኖተ ሰላም ከተማ የሚገኙ የስርዓቱ ታጣቂዎችና የልዩ ጥበቃ አባላት የተቃዋሚ ታጣቂዎች በአከባቢው ገብተዋል በሚል ጥበቃቸውን ከመቸውም ግዜ በላይ እንዲያጠናክሩ በአከባቢው የጸጥታ ሃላፊ ጥበቅ መመርያ መሰጠቱን ቷውቋል።
የስብሰባው ዓላማ ፤ በመላ አገሪቱ እያጋጠመው ባለ ህዝባዊ ተቋውሞ ስጋት ላይ የወደቀው የኢህአደግ መንግስት ጸጉረ ለወጥ በሚል የዜጎችን ሰብአዊ መብት በመግፈፍ ፤ ዜጎች ከቦታ ቦታ ተንቀሳቅሰው በመስራት ኑራቸውን እንዳይመሩ የሚያደርግ እንደሆነ ከስብሰባው ተሳታፊዎች የደረሰን ዘገባ ያመለክታል።