በትግራይ ክልል የሚገኙ ሚሊሻዎች እድሜን በማይለይ ሁኔታ በህወሃት ካድሬዎች
ቀጥታዊ አመራር በተከታታይ ወታደራዊ ስልጠና ላይ መጠመዳቸውን የገለጸው መረጃው በተለይ በእድሜ የገፉት አዛውንቶች ከዚህ በፊት
ያገለገልነው ይበቃናል፤ መሳርያችሁን ተቀብላችሁ አሰናብቱን በማለት ወደ ሚመለከታቸው የስርአቱ ባለስልጣናት ብሶታቸውን ቢያቀርቡም
የተሰጣቸው መልስ ቢኖር አገሪትዋን ማን ሊጠብቃት ትፈልጋላችሁ አናሰናብታችሁም በማለት ጥያቄያቸውን ውድቅ እንዳደረጉት የተገኘው
መረጃ አስታውቋል።
ስልጣን ላይ ያለው አምባገነኑ የኢህአዴግ ስርአት ከህዝቡ ተነጥሎ ስለሚገኝ
ካለበት ስጋት ተነስቶ ህዝቡን በመሳርያ ሃይል ለማምበርከክ በማሰብ ታጣቂዎችን በወተሃደራዊ ስልጠና ላይ ጠምዷቸው እንደሚገኝ በተደጋጋሚ
መግለፃችን ይታወቃል።