Wednesday, February 25, 2015

በሁመራ ከተማ “ምርጥ ገበያ” ተብሎ በሚጠራው መንግስታዊ ተቋም ተቀጥረው የሚሰሩ ወገኖቻችን ደመወዛቸው በጊዜው ስላልተከፈላቸው አድማ ማካሄዳቸው ታወቀ።



    ከከተማዋ የደረሰን መረጃ እንደሚያመለክተው ምርጥ ገበያ ተብሎ በሚጠራው የመንግስት ሸቀጦች ተሰማርተው እየሰሩ  የሚገኙ 120 የሚደርሱ ወገኖቻችን ደመወዛቸው ከሁለት ወር በላይ ሳይከፈላቸው በመቆየታቸው ምክንያት ጥር 29/2007 ዓ.ም ሸቀጣ ሸቀጥ አናራግፍም አንጭንም በማለት ተቃውሞ እንዳካሄዱ ለማወቅ ተችሏል።
  መረጃው እንደሚያስረዳው የተነሳው ተቃውሞ ወደ ከፍተኛ ደረጃ እንዳይሸጋገር የሰጉ የስርዓቱ ካድሬዎች ምን ያመጣሉ ከሚል የንቀት ባህሪያቸውና አስተሳሰባቸው የተንሳ ከልክለዋቸው የነበረውን ደመወዛቸውን በስቸኳይ ለመክፈል እንደተገደዱ ታውቋል።