የተገኘው መረጃ እንዳመለከተው በሶማሌ ክልል
ጅግጅጋ ከተማ በሚገኘው ዩኒቨርሲቲ ግንቦት 18/ 2007 ዓ/ም ሌሊት
ላይ የድምፅ ቆጠራ በተጀመረበት ግዜ ኢህአዴግ መሸነፉን ያረጋገጡት የስርዓቱ ካድሬዎች ሙሉ በሙሉ የድምጹን ቆጠራ ከመጠናቀቁ በፊት
6 ሰዓት ላይ ኮረጀውን በመከላከያ ሰራዊት ተሰርቆ መወሰዱን ለማወቅ ተችሏል።
የምርጫ ኮረጀውን የሰረቁት የምስራቅ እዝ፤ የ13ኛ ክፍለጦር
ወታደሮች እንደሆኑ የገለፀው መረጃው የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎቹ ድምፃችን ሆን ተብሎ በስርዓቱ ተጭበርብረዋል በማለት ወደ ሚመለከታቸው
የመንግስት አካላት ጥርያቸው ቢያቀርቡም ሰሚ ጀሮ እንዳላገኙና ተቃውማቸው እየቀጠሉ መሆናቸውን የተገኘው መረጃ አክሎ አስረድቷል።