በደረሰን መረጃ መሰረት በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ከመጋቢት ወር ጀምረው
በተከታታይ ለሦስት ወር ያህል ማስታወቂያ ቢወጣም ለመግባት ፈቃደኛ የሆነ ሰው ስለጠፋ ወደ ክልሎች ማስታወቂያው እንዲወጣ መደረጉን
ለማወቅ ተችሏል።
በአገራችን ውስጥ በኢህአዴግ አመራሮች ስጋት ምክንያት ነባር ፖሊሶችን
ከጠላት ጋር ግንኙነት አላችሁ እየተባሉና የያዙት ሞባይል በየቀኑ እየተፈተሸ በርካታ ወጣቶች በመታሰራቸው ምክንያት አዲስ ፖሊሶች
ለመቅጠር የወጣውን ማስታወቂያው ህዝቡ እንዳልተቀበለው መረጃው አክሎ አስረድቷል።