Monday, May 21, 2018

በዚህ ሳምንት በርከት ያሉ አዲስ ምልምል ሰልጣኞች የወያኔ ኢህአዴግ ጨቋኝ አገዛዝ በመቃወም ወደ ትህዴን ትምህርትና ስልጠና ክፍል ተቀላቀሉ።

አዲስ ከመጡ ምልምል ሰልጣኖች የተወሰኑትን ለመጥቀስ ያህል፦
1.  ሃፍቶም መብራህቱ ወልደብርሃን በመቐለ ዞን፣ ሰሓርቲ ሳምረ ወረዳ፣ ማርያም ምቖ ቀበሌ ነዋሪ የነበረ
2.  ኢፍሬም ገብረሚካኤል አስመላሽ በማእከላዊ ዞን፣ አሕፈሮም ወረዳ፣ ዓዲ ዛታ ቀበሌ ነዋሪ የነበረ 
3.  ናትናኤል ወሉ ገብረስላሴ ምዕራባዊ ዞን፣ ቃፍታ ሑሞራ ወረዳ፣ ትርካን ቀበሌ፣
4.  መለስ ሃይለስላሴ ገብረስላሴ ማእከላዊ ዞን፣ ዓብዪ ዓዲ ወረዳ፣ 03 ቀበሌ፣
5.  ገብረዋህድ ነጋ በለጠና ኣክሊሉ ተስፋይ ፍሰሃ፣ ሁለቱም ከማእከላዊ ዞን፣ ዓድዋ ወረዳ፣ 04 ቀበሌ፣
6.  ክብሮም ማሙ ገረዝጊሄር፣ ሰሜን ምዕራብ ዞን፣ ታሕታይ ኣድያቦ ወረዳ፣ ዋዕላ ንህቢ ቀበሌ፣
7.  መለስ ገብረሂወት ተስፋይ ከማእከላዊ ዞን፣ ዓድዋ ወረዳ፣ ወዲቐሺ ቀበሌ፣
8.        ዓብለሎም ካሳ ሓጎስ ማእከላዊ ዞን፣ መረብ ለኸ ወረዳ፣ ምሕቛን ቀበሌ፣
9.  ገርዝጊሄር መብራህቱ ገረመድህን ከማእከላዊ ዞን፣ ወርዒ-ለኸ ወረዳ፣ ማእከል ሰግሊ ቀበሌ፣
10. ባና ተወለ ዮሃንስ ሰሜን ምዕራብ ዞን፣ ላዕላይ አድያቦ ወረዳ፣ ጎዲፋይ ቀበሌ የሚኖሩ የነበሩ ሲሆኑ፣ ወደ ትጥቅ ትግል ጎራ እንዲሰለፉ ያስገደዳቸው ምክንያት ሲገልፁ፣ በዴሞክራሲና በስራ እጦት ምክንያት እንደሆነ ያስረዳሉ።

በተለይ ገብረዝጋብሔር መብራህቱ በግሉ የደረሰው በደል ስያስረዳ፣ የሚታረስና  የመኖርያ ቦታ እንዲሰጠው ጠይቆ አወንታዊ ምላሽ እንዳላገኘና ከቦታ ቦታ ተንቀሳቅሶ እንዳይሰራ ደግሞ ከየት መጣህ፤ የት ነበርክ፤ ከተቃዋሚ ድርጅቶች ጋር ግንኙነት ታደርጋለህ በማለት የስርአቱ ታማኝ ካድሬዎች ሊያሰሩት እንዳልቻሉ ገልጿል። ይሄን ሁሉ ችግር እየተቋቋመ ሰርቶ ደግሞ ክፍያው ከማነሱ የተነሳ ገንዘብ ለመቆጠብ ይቅር ለእለት ጉርሻው እንኳን እንደማይበቃው ያስረዳል። 
   ወጣቶቹ በመጨረሻ ያስተላለፉት መልእክት፣ በዴሞክራሲና በስራ እጦት ምክንያት እየተሰቃየህ ያለሀው ኢትዮጵያዊ ወጣት አንገት ደፍተህ በማንባትና በስደት የሚመጣ ለውጥ የለም። መፍትሄ ሊሆን የሚችለው ከትህዴን ጎን ተሰልፈህ ወያኔን መፋለም ብቻ እንደሆነ ይመክራሉ። 

No comments:

Post a Comment