Monday, April 28, 2014

የ22ኛ ክፍለ-ጦር አባል የሆነውና መጋቢት 28 ቀን 2006 ዓ/ም ለተገደለው ወታደር በማስመልከት ገዳዩ ተይዞ ለምን ወደ ፍርድ አይቀርብም ብለው ለጠየቁ የሰራዊቱ አባላት አድማ አነሳሳታቹሃል ተብለው በላያቸው ላይ አስተዳደራዊ በደል እየደረሰባቸው መሆኑ ተገለፀ።



በ22 ክፍለጦር በስታፍ ውስጥ እየሰራ የነበረው መቶ አለቃ ደረጀ ካሳየ የተባለው መኮንን መጋቢት 28/ 2006 ዓ/ም የተገደለ ሲሆን አባላቱ ገዳዩ ተይዞ ለምን ወደ ፍርድ አይቀርብም ብለው ቢጠይቁም ጉዳዩ ተደበስብሶ እንዲቀር የሚፈልጉ የክፈለጦሩ አዛዦች ግን ጥያቄ ላቀረቡ አባላት አድመኞች በሚል ምክንያት ከወር ደሞዛቸው 5% ቀጥተው ከነበሩበት ክፍል አስወጥተው እንደበተንዋቸው ለማወቅ ተችለዋል።
   በመረጃው መሰረት እነዚህ ዴሞክራሲያዊ ጥያቄ በማቅረባቸው ብቻ አድመኞች ተብሎው የተቀጡና ከክፍላቸው ወጥተው እንዲበታተኑ የተደረጉ የሰራዊት አባላት መቶ አለቃ አስራት ተሾመ፤ አስራ-አለቃ አቡ ማርቆስና ሌሎችም እንደሆኑና የተወሰደው እርምጃም በመላው የክፍለጦሩ የሰራዊት አባላት መነሳሳት እንዳስከተለ መረጃው አክሎ እስረድተዋል።
   ይህ በእንዲህ እንዳለ ሻለቃ መብራህቱ የተባለው የ 8 ሜካናይዝድ የመረጃ ሃላፊ ሰራዊቱን በማነሳሳትና ጥይት በመሸጥ ውንጀላ ተከሶ አዲ ኮኾብ በተባለው የእዙ እስርቤት ውስጥ ታስሮ እንደሚገኝ ከእስርቤቱ ውስጥ ከተገኘው መረጃ ለማወቅ ተችለዋል።