በመረጃው መሰረት እየተካሄደ
በነበረው ስብሰባ ላይ ፖሊስ ተተኳሽ ነገሮችን በመሽጥ፤ ጉቦ በመቀበል፤ ሰዎችን በኮንትሮባንድ ወደጎረቤት ሃገር በማሸጋገር ቀዳሚውን
ቦታ ይይዛል ብለው በስብሰባው ላይ ተካፋይ የነበሩ አንዳንድ ወገኖች በሚገመግሙበት ግዜ ወዲ ሻምበል በሚል ቅጥያ ስም የሚታወቀው
ዘአማኔል የተባለው የትግራይ ክልል የፖሊስ ሃላፊ ስብሰባውን ረግጦት እንደወጣ ሊታወቅ ተችሏል።
በተመሳሳይ ከተሳታፊዎቹ አንዱ የሆነው የትግራይ ሰሜናዊ ምዕራብ ዞን የፖሊስ
አዛዥ ኮማንደር ገብረኪዳን ወዲ ሽራሮ በበኩሉ ህዝብ ሰብስባችሁ ክ-ከምታዋርዱን ለብቻችን ለምን አትገመግሙንም በማለት ስብሰባውን
አቋርጦት እንደወጣ መረጃው አክሎ አስረድቷል።