Monday, September 22, 2014

በነቀምትና ወለጋ ከተማ የሚገኙ ከዚህ በፊት ወታደሮች የነበሩ ዜጎች ለመስሪያ የሚውል ቦታ ይሰጠን ብለው ያቀረቡት ጥያቄ ከአስተዳዳሪዎች ተገቢ ምላሽ ባለማግኘታቸው ምክንያት ምሬታቸው በመግለጽ ላይ እንደሚገኙ ተገለጸ።



    እነዚህ በነቀምትና ወለጋ ከተማ የሚገኙ በውትድርና የነበሩ ወገኖች እያጋጠማቸው ያለውን የኑሮ ችግር ለማቃለል በማለት በማህበር ተደራጅተው መስራት የሚችሉበትን ቦታ ይሰጠን ብለው ላቀረቡት ጥያቄ በአስተዳደሩ ተገቢውን ምላሽ እንዳላገኙ የገለጸው መረጃው በዚህ  ምክንያትም ወደ ስደት እያመሩ መሆናቸውን ለማወቅ ተችሏል።
    መረጃው ጨምሮም የከተማው አስተዳዳሪዎች ወታደሮቹ ተደራጅተው መስራት ከጀመሩ በመንግስት ላይ አደጋ ሊፈጥሩ  ይችላሉ በማለት ማህበሩ እንዲፈርስ ከፍተኛ ጥረት ያደርጉ  እንደነበር የገለጸው መረጃው ስራ የፈቱ  ወታደሮችም ባልተፈለገ ስፍራዎችና ለመጠጥ ስሶች ተጠቂ ሆነው እንደሚገኙ መረጃው ጨምሮ አስረድቷል።