ከአካባቢው በደረሰን መረጃ መሰረት እነዚህ ቀደም ሲል በትግል የቆዩና በጡረታ
ተሸኝተው በተምቤን አብይ ዓዲ ከተማ በማህበር ተደራጅተው ኑሮአቸውን ሲመሩ የቆዩ ዜጎች፤ ራሳቸው ተደራጅተው ሲሰሩ ከቆዩበት ስራ፤
ያለምንም ምክንያት 5 ነባር ታጋዮች በወያኔ ኢ.ህ.አ.ዴ.ግ ባለስልጣናት ሴራ እንደተባረሩ ተገለፀ፣
እኚህ ወገኖች “እኛ ንፁሃን ዜጎች እያለን ለምን ከስራችን ተባረርን።” በማለት
ዮናስ ወደ ተባለ የወረዳው አስተዳዳሪ በጠየቁበት ጊዜ ተገቢ ምላሽ ስላልሰጣቸው እንዳማራጭ በኮብልስቶን ስራ እንዲሰማሩ ያቀረቡት
አቤቱታም ሰሚ ጆሮ እንዳላገኘ ሊታወቅ ተችሏል፣