በወልቂጤ አካባቢ ሁራአክሊል ሃዋሪያ በተባለው ወረዳ በሚገኙ የመንግስት ሰራተኞች
ላይ ከፍተኛ ማስፈራራት እየደረሰባቸው መሆኑን የገለፀው መረጃው የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አለም ይርጋና የወረዳው የድርጅት ጉዳይ
ሃላፊ አንድ ላይ በመሆን በማስፈራራት ተግባር ላይ ተጠምደው እንደሚገኙ ለማወቅ ተችሏል፣
ማስፈራራት እየደረሰባቸው ከሚገኙ የሌላ ክልል ተወላጆች የወረዳው ሰራተኞች
መካከል ይሁን የተባለው የወረዳው የግብርና ጽሕፈት ቤት የግብዓት የስራ ሂደት ባለሙያና ለጊዜው ስማቸው እንዲጠቅስ ያልፈለጉ የትምህርት ጽሕፈት ቤት ሰራተኞች
ከመጋቢት 11 /2007 ጀምሮ የምርጫ ካርድ ካለማውጣታቸው ጋር ተያይዞ እንደሚባረሩ በክልሉ መስራት እንደማይችሉ አለምሰገድ በተባለ
የስርዓቱ ተላላኪ የተነገራቸው መሆኑን ለማወቅ ተችሏል፣