Friday, May 6, 2016

የብአዴን ከፋተኛ አመራር ባለፈው ሳምንት ከክልሉ ተወላጅች ለመወያየት ዳላስ በሄዱበት ወቅት በከባድ ወጥረት ውስጥ ገብተው የአሰቡትን ሊሳካላቸው እንዳልቻለ ተገለፀ።



የደረሰን መረጃ እንደሚያመለክተው በማያዚያ 17/ 2008 ዓ/ም የብአዴን ከፋተኛ  አመራሮች ወደ አሜሪካ አገር ሂደው የአማራ ተወላጆችን በልማት ዙሪያ ያተኮረ ወይይት ለማደረግ በሚል   የታሰበ ስብሰባ በብአዴን ተወካዮች በዳላስ ዋሽንግተን ዲሲ   በኢትዮጵያ አምባሲ የተካሂደ ሲሆን የተሰበሰቡበትን አዳራሽ ደግሞ የጠነከረ ጥበቃ የተደረገበት እንደነበረ የገለፀው መረጃው በርከት ያሉ የአማራ ተወላጆች ትኪት ያላቹሁም እየተባሉ መከልከላቸዉን ለማወቅ ተችለዋል።
 የዚህ ዋና ምክንያት ደግሞ በአዳራሹ ውስጥ ከገቡ በኋላ አንደበታዊና ያልታሰበ  ተቃውሞ ሊነሳ ይችላል ብለው ሰጋት የወደቁ የብአዴን አመራሮች ከ50 ሺ በላይ ኢትዮጵያዊያን የሚገኙበት ዳላስ ከ45 የማበልጡ ሰዎች ብቻ ያነጋገሩ በመሆናቸው ከህዝብ ተነጥለው እንዳሉ የሚያመልከት እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል።
   የሰብሰባው ዋና አስተባባሪ የነበሩት ደግሞ ፀሃይ ፃደቅ አብራሂም ሙሉ ጎጃም ገዳሙ አቶ መሰረት ወ/ሮ መሰረት አያሌው አረጋው ወ/ሮ አለምፀሃይና ሌሎች የስርአቱ አመራሮች ሲሆኑ ያካሄዱት  ሰብሰባ ደግሞ በከባድ ሰጋትና ጥበቃ ዉስጥ ሆነው እንዳካሄዱትና እንዳሰቡት ያለመካሄዳቸዉን ያገኘነው መረጃ ጨምሮ  አስረድተዋል።


No comments:

Post a Comment