Wednesday, November 30, 2016

በዚህ ሳምንት በርከት ያሉ የጎንደር ዩኒቨርስቲ የሕክምና ተማሪዎች ዲፓርትመንቱ ይቀየርልን ብለው ጥያቄ ስላቀረቡ ብቻ በፀጥታ ሃይሎች ታፍነው ወደ አልታወቀ ስፍራ መወሰዳቸው ታወቀ።



በመረጃው መሰረት የጎንደር ዩኒቨርስቲ የህክምና ዲፓርትመንት  ተማሪዎችስራ የማግኘት እድላችን  በመናመኑ ምክንያት ሌላ ዲፓርትመንት ይቀየርልን ስላሉ ብቻ  የአስቸኳይ  የግዜ ኣዋጅ መምርያ  ጥሳችህዋል በሚል ስንካል ምክንያት  በህዳር 19 ቀን 2009 ዓ/ም  102 ተማሪዎች በፈደራል ፖሊስ  ታፍነው ወደ ኣልታወቀ ስፍራ እንደተወሰዱና  እስከ አሁንም  የት እንደገቡ ኣልታውቀም በማለት  ከተማሪዎቹ  በኣማርኛ ለሚሰራጨው  ሬድዮ ኣሜሪካ   ከሰጡት ቃል  ለማወቅ ተችለዋል።፣
  የጎንደር ዩኒቨርስቲ አስተዳዳሪ  በበኩላቸው  የተማሪዎቹ ተገን ከመሆንና ጥያቄዎቻችውን ስምተው ተገቢውን ምላሽ ከመስጠት  ፈንታ ከስርኣቱ ፀጥታ ሃይሎች  በመተባበር  ተማሪዎችን በሃይል ኣፍነው እንዲወሰዱ  አድርገዋል ያሉት ተማሪዎቹ  በዚህ የተነሳ ደግሞ  በጎንደር ከተማ  በተለይ ደግሞ  በጎንደር ዩኒቨርስቲ  ከፍተኛ ውጥረት ነግሰዋል በማለት ተማሪዎቹ ጨምረው ገልፀዋል።    

No comments:

Post a Comment