Wednesday, April 9, 2014

የኢ.ህ.አ.ዴ.ግ ባለስልጣኖች የስልጣን ጌዜያቸውን ለማራዘም በማሰብ ወደ ማሰልጠኛ ለሚሄዱ ምልምል ወታደሮች አስመልክተው የሚያወጡትን ማስታወቅያ በህዝብ ላይ ተቃውሞ እያጋጠማቸው እንደሆነ ከተለያየ አካባቢ የተገኘ መረጃ አመለከተ።



በመረጃው መሰረት የኢ.ህ.አ.ዴ.ግ ባለ ስልጣናት ከህዝቡ ሊያጋጥማቸው የሚችል ተቃውሞ በመሳርያ ሃይል ለመጨፍለቅና የስልጣን ግዝያቸውን ለማራዘም ብለው በርከት ያሉ ወጣቶች መልምለው ብር ሸለቆ ማሰልጠኛ ውስጥ ለማስገባት ያሰቡትን እቅድ በኢትዮጵያ ህዝብ ተቃውሞ እያጋጠማቸው ባለበት ባሁኑ ግዜ እቅዱን ተግባራዊ ለማድረግ ከ8 ክፍል በላይ ለሆኑ ወጣቶች መቀሌ ከተማ ውስጥ ለሚገኙ ያካባቢ መስተዳድሮች እያንዳዳቸው 1,600 ወጣት መልምለው እንዲያቀርቡ ጥብቅ ትእዛዝ ቢሰጣቸውም ለቀረበላቸው ትእዛዝ በመቃወም ወጣቶቹ ወደ አ/አበባና ሌሎች ያገራችን ከተሞች እየሸሹ መሆናቸው ለማወቅ ተችለዋል።
     ያካባቢ መስተዳድሮቹ ወጣቶቹን ወደ ውትድርና ለመመልመል ለተሰጣቸው መመርያ ከህዝቡ ተቃውሞ ስላጋጠማቸው 10 ክፍል ጨርሰው ስራ ላጡና የጎዳና ተዳዳሪዎች ለሆኑ ወጣቶች በመሰብሰብ ስራ እንፈጥርላቹሃለን ተመዝገቡ ብለው በማታለል ወደ ወትድርና ለማስገባት ሞክሮው ሊሳካላቸው እንዳልቻለ መረጃው አክሎ አስረድተዋል።