በጋምቤላ ከተማ የሚታየውንና እስካሁን ድረስ መፍትሄ ያላገኘው የመሰረተ ልማት ችግር እንዲቀረፍላቸው በተደጋጋሚ
ለሚመለከታቸው የመንግስት አካላት አመልክተው የተሰጣቸው መፍትሄ ባለመኖሩ በሽዎች የሚቆጠሩ የከተማዋ ኗሪዎች ጉንበት
27,2005 ዓ/ም ባካሄዱት ሰላማዊ ሰልፍ አንድ ላይ በመሆን በስርዓቱ ላይ ያላቸውን ቅሬታ መግለጻቸውን ቷውቋል።
ሰላማዊ ሰልፉ በከተማዋ ከሚታዩ ችግሮች ጋር የተያያዘ ቢሆንም በቅርቡ በአ/አበባ ከተማ ከተደረገው በሰማያዊ
ፓርቲ የተመራ ሰላማዊ ሰልፍ ግንኝነት እንዳለው ከአከባቢው የደረሰን ዘገባ ያስረዳል።
መንግስት
በሰላማዊ ፓርቲ መሪነት በአ/አበባ ከተማ የተካሄደውን ሰላማዊ ሰልፍ ተከትሎ በሌሎች ክልሎችም ሊቀጥል ይችላል የሚል ስጋት ስላደረበት
የተቋውሞ ሰልፍ ሊቀሰቀስባቸው ይችላል በሚላቸው አከባቢዎች በርካታ የፌደራል ፖሊስ አባላት በማሰማራት ላይ መሆኑን ቷውቋል።