Wednesday, June 5, 2013

በአዊ ዞን ባልታወቁ ሰዎች የሚገደሉ ዜጎች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተበራከተ መምጣት የአከባቢውን ኗሪ ህዝብ ስጋት ላይ ጥሎታል።



በዞኑ በጉንበት ወር ብቻ ስድስት የአከባቢው ኗሪዎች ማንነታቸው ባልታወቁ ሰዎች ተገድለው የተገኙ ሲሆን ፤ ወንጀለኞቹ ሰዎችን ለመግደል የሚገለገሉበት መሳሪያም ፤ ከመንግስት የጸጥታ አካላት በኪራይ መልክ የሚያገኙት ሆኖ ፤ ዘርዝፊዎቹ ከሟቸቹ የሚገኘውን ገንዘብ ከአከባቢው የጸጥታና የመስተዳድር አካላት ጋር አብረው እንደሚካፈሉት የደረሰን ዘገባ ያስረዳል።
ይህ በእንዲህ እያለ በሽንዲ ከተማ ሰላማዊ ሰው የገደሉ የስርዓቱ ታጣቂዎች በነጻ መለቀቃቸውን ቷውቋል ።
በአዊ ዞን ሽንዲ ከተማ አቶ ይሁን ደምመላሽ የተባሉ ንጹህ ዜጋን አሸባሪ በሚል ሰበብ ከገደሉት የኢህአዴግ ታጣቂዎች መካከል፣-
1-ኮንስታብል ብርሃኑ ሽፈራው
2-ኮንስታብል ለአለም
3-ሚሊሽያ ደሳለው ማሙ
4-ሚሊሽያ ክንዴ ይርጉ የሚገኙባቸው ሲሆን ለምን በነጻ ተለቀቁ የሚል ጥያቄ ከህዝቡ እንዳይነሳ ለግዜው በፖሊስ ቁጥጥር ስር እንዲውሉ በማድረግ መርማሪ ፖሊስ ኢንስፔክተር ደረጀና ዋና አስተዳደር ሙላቱ ጌታሁን የሚገኙበት የአከባቢው የፖሊስ ጽ/ቤት ፤ አቃቢ ህግና ፍርድ ቤት በመመሳጠር በነጻ እንዲለቀቁ ማድረጋቸውን ለማወቅ ተችሏል።