በአብደልራፍዕ ከተማ
የሚገኙ አስተዳዳሪዎችና ፖሊሶች በቀን ስራ ላይ ለተሰማሩ ሰራተኞች ስራ ላይ ውለው ወደ ቤታቸው ሲመለሱ መንገድ ላይ ጠብቀው
200 ብር እንዲከፍሉ በማስገደድ እንደሚያስሯቸው የገለጸው መረጃው ከታሰሩት መካከልም አስራት ማስረሻ የተባለው ወጣት 200 ብር
መክፈል አልችልም ብሎ ወደ እስርቤት ከሄደና ከእስርቤቱ በሌሊት አውጥተው ሲደበድቡት ለማምለጥ በሞከረበት ሰአት ሳጅን አወቀ ክንዱ
የተባለው ፖሊስ ቶኩሶ እንደገደለው ለማወቅ ተችሏል፣፣
መረጃው ጨምሮ እንደገለፀው በአስተዳዳሪዎቹና በፖሊሶቹ ተግባር የተቆጣ
የአብደራፍዕ ከተማ ህዝብ ላቡን አፍስሶ የሚኖር ንፁህ ዜጋ 200 ብር
መክፈል አልችልም በመለቱ ብቻ እንዲገደል መደረጉ ሰብአዊነት የሌለው ተግባር ነው ሲሉ ብሶታቸውን እየገለፁ መሆናቸውን መረጃው አክሎ
አስረድቷል፣፣