Wednesday, August 20, 2014

በመቐለ ከተማ ውስጥ በሁሉም ክፍለ ከተሞች የሚኖር ህዝብ ፍትሃዊነት በሌለው የግብር አሰባሰብ ምክንያት እሮሮውን እየገለፀ መሆኑን ምንጮቻችን ከከታማዋ አስታወቁ።



በመረጃው መሰረት በሰባቱ የመቐለ ክፍለ ከተሞች የሚገኝ ነዋሪ ህዝብ ፍትሃዊነት በጎደለው የስርዓቱ የግብር አሰባሰብ ችግር ላይ በመውደቁ ምክንያት አቶ ገብረገርግስ ገብረማሪያም ወደ ተባለው አስተዳዳሪ በመሄድ “እኛ ይህን የሚያክል ገንዘብ ልንከፍል አቕም የለንም’’በማለት ብሶታቸው ቢያቀርቡም የመንግስት ግብር የመክፈል ግዴታቹሁ ካሟላቹሁ በኋላ ልትከሱ ትችላላቹሁ አሁን ግን ስራ ስላለኝ ልሳማችሁ አልችልም በማለት እንዳባረራቸው ለማወቅ ተችሏል።
    እነዚህ ወጎኖች በፊናቸው ለማይረባ የሸቀጣሸቐጥ ስቁቻችንን ውረሱት እንጂ ዛሬም ይሁን ነገ አንከፍልም በማለት ተቓውሞ ማሰማታቸውን የደረሰን መረጃ አክሎ አስረድተዋል።