Monday, October 27, 2014

በዓብይ ዓዲና በሃውዜን ከተሞች እንዲፈርሱ በተወሰነባቸው የመኖሪያ ቤቶች ካሳ ለመክፈል አድሎ እየተፈፀመ እንደሆነ ምንጮቻችን ከስፍራው አስረድተዋል፣




እነዚህ በዓብይ ዓዲና ሃውዜን ከተሞች የሚገኙ በማስተር ፕላን ስም እንዲፈርሱ የተወሰነባቸው መኖሪያ ቤቶች ካሳ የሚሆን ክፍያ ለመክፈል ለባለቤቶች ከ500 ሺህ እስከ 600 ሺህ ብር ለቤት መስሪያ የሚውል መሬት ሊሰጣቸው መሆኑ በስርዓቱ ካድሬዎች የተገለፀላቸው ቢሆንም። በተግባር ግን በጉቦና በአድሎ እየተፈፀመ መሆኑን ጨምረው ገልፀዋል፣
   ይህ በእንዲህ እንዳለ ለአስተዳዳሪዎች ጉቦ መክፈል ያልቻሉ 200 ሺህ ብር ብቻ ሲከፈሉ ጉቦ ለከፈሉት ግን ከ500 ሺህ ኣስከ 600  ሺህ ብር ካሳ ከተከፈሉ በኋላ በአግባቡ ያልተከፈሉ ወገኖች ግን ይህ አካሄድ ትክክልና ፍትሃዊ ስላልሆነ ቤታችንን አናፈርስም በማለት ተቃውሞ እያካሄዱ መሆናቸውን ለማወቅ ተችሏል፣