በገዥው መንግስት የተሰማሩ ተላላኪ የክልሉ ልዩ ሃይሎች በነዋሪው ማህበረሰብ
ላይ አረመኔያዊ ግፍ እየፈፀሙ መሆናቸውና በከማሽ ዞን በሎጂ-ጋንፎ ወረዳ የሚገኙ ነዋሪዎች ተንቀሳቅሰው ዕለታዊ ስራዎቻቸውን መስራት
እንዳልቻሉ የገለፀው መረጃው እንደአብነትም በሎጆ-ጋንፎ ወረዳ የምርጥ ዘር ድርጅት አምራች የሆኑ ኢንቨስተሮችንና ነጋዴዎችን የካቲት
3 ቀን 2007 ዓ/ም የክልሉ ልዩ ሃይል ታጣቂዎች በመያዝ ያለምንም ምክንያት አስረው ማሳደራቸውንና በኋላም ጉቦ እንዲከፍሉ በማስገደድ
ሊፈቷቸው እንደቻሉ ሊታወቅ ተችሏል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ የካቲት 2 ቀን 2007 ዓ/ም 3 የተቃዋሚ ፓርቲ
አባላት የሆኑ ወጣቶችን አሸባሪዎች በሚል ምክንያት አሶሳ እስር ቤት በመወሰድ እያሰቃዩዋቸው መሆኑን ከስፍራው የደርሰን መረጃ አክሎ
አስረድቷል።