Wednesday, February 3, 2016

በጋምቤላ ክልል በአኝዋክ ብሄረሰብና በንዌር መካከል ያጋጠመውን ግጭት በርከት ያለ የሰው ህይወት እንደጠፋ ተገለፀ።



ያገኘነው መረጃ እንደሚያመለክተው፣ በአኝዋክና በንዌር ብሄረሰብ መካከል የተከሰተውን ከባድ ግጭት ቀደም ሲል የሞቱትን ከ20 በላይ ደርሶ እንደነበረ ጠቅሶ ግጭቱም በአሁኑ ጊዜ እየቀጠለ እንዳለ ይህ ደግሞ የሞቱትን ቁጥር ሊጨምር እንደቻለ ያገኘነው መረጃ አስረድቷል።
የዜና አውታሮች ነዋሪዎችን መሰረት በማደረግ እንደዘገቡት-በግፅቱ ምክንያት በርከት ያሉት ቤቶች ንደተቃጠሉ ከገለፀ በኋላ ይህንን ተከተሎ ደግሞ የመንግስት ፅህፈት ቤቶችን ጨምሮ ባንክ ቤቶችን እንዲሁም የግል ድርጅቶች የተዘጉ ሆነው ለብዙ ቀናት ያህል የቀጠለ ግጭት የክልሉ የትራንስፖርት ሃላፊውን ጨምሮ የ8ት ሰዎች ህይወት እንደጠፋ ሲሆን በከተማው በሁለት ቦታዎች የቦምብ ፍንዳታ አደጋ ያጋጠመ ሆኖ የክልሉ ፖሊስ አባላትና የመከላከያ ሰራዊት አባላት ጨምሮ ሁኔታውን ኦለማረጋጋት በማለት ተሰንማረተው በህዝቡ ዘንድ ውጥረትና ግርግር ሊፈጥሩ ኣንደቻሉ ለማወቅ ተችሏል።
አግጭቱ መንስኤ ደግሞ ከ15 ቀናት በፊት በክልሉ ጤና ሳይንስ ኮለጅ ምክትል ዲንና በምክትል ፕሬዝዳንት የሆነውን አንድ ሽፌር መካከል  ባጋተመው ግጭት የተነሳ ሲሆን፣ የአኝዋክ ተወላጅ የሆነውን ሽፌር በጥይት ተኩሶ እጁን የመታው ሲሆን፣ ብዚህ ደግሞ የብሄር ግጭት መልክ ልይዝ እንደቻለ የተገኘው መረጃ ጨምሮ አስረድቷል።

No comments:

Post a Comment