Wednesday, May 2, 2018

የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን ከኢንሹራንስ ኩባንያዎች ጋር ቅድመ ሁኔታ የሌለበት ዋስትና ከመስጠት ጋር ተያይዞ፣ እየወሰደ ያለው ዕርምጃ ቅሬታ አስነሳ፡፡



ባለሥልጣኑ ከአራት ዓመታት በፊት የዋስትና ሰጪ (ኢንሹራንስ) ኩባንያዎች፣ መስጠት ያቆሙትን ቅድመ ሁኔታ የሌለው ዋስትና እንዳይሰጡ መከልከሉ ይታወሳል፡፡ ነገር ግን ከዚህ ቀደም ከቀረጥ ነፃ የገቡ በተለይም የኮንስትራክሽን ማሽነሪዎች፣ ተሽከርካሪዎች፣ እንዲሁም አገልግሎቶቻቸውን ሲጨርሱ ከአገር እንዲወጡ የሚጠበቅባቸው ተመሳሳይ ዕቃዎች ላይ ያልተሰበሰቡ ግብርና ቀረጥ ለመሰብሰበ ዕርምጃ መውሰድ መጀመሩ ይታወሳል፡፡
  በዚህም ዕርምጃ የቃሊቲ ቅርንጫፍ ብቻ ከ160 ሚሊዮን ብር በላይ ከአገር ውስጥ ኢንሹራንስ ኩባንያዎች መሰብሰብ ችሏል፡፡ ይህንን ዕርምጃ ለመውሰድም በሚል ባለሥልጣኑ በጊዜያዊነት የአንዳንድ ኢንሹራንስ ኩባንያዎችን የባንክ አካውንት እንዳይንቀሳቀስ አግዶ ነበር፡፡   
  በዕርምጃው ምክንያት የኢንሹራንስ ኩባንያዎች በማኅበራቸው አማካይነት ቅሬታቸውን ለባለሥልጣኑ አስገብተው ነበር፡፡ በቅሬታቸውም መሠረት አንዳንድ ኢንሹራንስ ኩባንያዎች ባልሰጡት የዋስትና ሰነድ ሌላ ድርጅት ዋስትና የሰጠበትን ዕዳ እንዲከፍሉ የሚጠየቁበት አሠራር መኖሩን፣ ዋስትና የተሰጠበት ዕዳ አልተከፈለም በሚልም የድርጅቶቹ የባንክ ሒሳብ ሲታገድ ከዕዳው ጋር ተመጣጣኝ ገንዘብ ሲገባው የድርጅቶቹ ገንዘብ በሙሉ የሚታገድበት ሁኔታ መኖሩን፣ እንዲሁም የኢንሹራንስ ኩባንያዎቹ የተጠየቀውን ዕዳ ከፍለው ገንዘባቸውን ከአስመጪው ለማስመለስ በሚያደርጉት ጥረት፣ ባለሥልጣኑ ትብብር እንደማያደርግላቸው የኢንሹራንስ ኩባንያዎቹ ቅሬታቸውን ገልጸዋል፡፡


No comments:

Post a Comment