Friday, September 4, 2015

በሑመራ ከተማ የሚገኙ ባለሃብቶች የትጥቅ ትግል በሚያካሂደው አርበኞች ግንቦት 7 የተገደሉትን የኢህአዴግ ሰራዊት አዛዦች ለቤተስባቸው የሚሆን ገንዝብ እንዲያዋጡ እየተገደዱ መሆናቸው ተገለጸ።



    ባለፈው ግዜ በትግራይ ምእራባዊ ዞን አካባቢ የትጥቅ ትግል በሚያካሂደው አርበኞች ግንቦት 7 ለተገደሉት የመከላከያ ሰራዊት አዛዦች ቤተሰቦች የሚሆን ገንዘብ እንዲያዋጡ ሑመራ ከተማ ለሚገኙ ባለሃብቶች እያስገደዷቸው መሆናቸውንና በርካታ ገንዘብ ተዋጥቶ እየተሰበሰበ መሆኑን ምንጮቻችን ከቦታው አስታወቁ።
    የአርበኞች ግንቦት 7 ድርጅት በስርዓቱ የመከላከያ ሰራዊት ላይ በወሰደው የማጥቃት እርምጃ ከሞቱት ወታደሮች መካከል ኮለኔል ወልደሚካኤል የተባለ የሚገኝባቸው አዛዦች ለቤተሰቦቻቸው የሚሆን ገንዘብ የዞኑ አስተዳዳሪዎች ከባለሃብቶች በግድ እየሰበሰቡ መሆናቸውን መረጃው ጨምሮ አስረድቷል።