Wednesday, March 16, 2016

በማይ ጨው ከተማ የሚገኙ የዓረና ተቃዋሚ ድርጅት አባላት በስርአቱ ካድሬዎች የማስፈራራት እርምጃ እየደረሰባቸው እንዳለ ተገለፀ።



ምንጮቻችን ከከተማዋ እንደገለፁት፣ ሰላማዊን ትግል አምነው እየተታገሉ ያሉት በትግራይ ክልል ደቡባዉ ዞን ማይ ጨው ከተማ የሚገኙ የዓረና ተቃዋሚ ድርጅት አባላት በስር አቱ ካድሬዎች ግፍ እየደርሰባቸ እንደሚገኝ ከገለፀ በኃላ፣ ይሁን እንጂ የገዢው ስርአት ካድሬዎች እየተክተሉት ያሉትን የማስፈራራት እርምጃ በመፍራት ትግላቸው እንደማያቛርጡት አባላቶቹ ብምሬት ገልፀዋል።
መረጃው ጨምሮ እንደገለፀው፣ በማይ ጨው ከተማ የሚገኙ የዓረና ተቃዋሚ ድርጅት አባላት የሆኑት ሰዎች፣ በስር አቱ እየደረሰባቸው ያለ የማስፈራራት እርምጃ ለመጥቀስ ያህል፣ ለህይወታችሁ እዞኑላት። ከድርጅቱ ውጡ፤ ለህዝባችሁ ይቅርታ ጠይቁ፤ የዓረና አባላት የሆኑት ብማይ ቸው ከተማ የሚያስተምሩ መምህራን ኣንዳታከራይዋቸው፤ ለሚስቶቻቸው ደግሞ ፍቷዋቸው ወይ ደግሞ እንገድላችሃለን የሚሉና ሌሎች እንደሆኑ በመጠቀስ፣ ከነዚህ የማስፈራራት ተግባር በመስራት ላይ ከሚገኙት ካድሬዎች ደግሞ የድምፂ ወያኔ ጋዜጠና የሆነው ሽሞይ ረብሶ የተባለ እንደሚገኙባቸው መረጃው አክሎ ገልፀዋል።



No comments:

Post a Comment