Monday, April 25, 2016

ገዥው የኢህአዴግ ስርአት ኣስጊ ሊሆኑ ይችላሉ ያልዋቸውና ለጠረጠርዋቸው ሰዎች፣ ማንኛውንም እንቅስቃሴዎቻቸው ለመቆጣጠርና ለመከታተል ሊያመቻቸው የኮምፒተር የወንጀል መቅጫ ረቂቅ ህግ ወደ ፓርላማ ማቅረባቸው ታወቀ።



  የኢህአዴግ ቡዱን ስልጣን ከያዘ በኋላ ለስልጣኔ ኣስጊ ናቸው ያልዋቸው ለመቆጣጠር በሚያመቻቸው መንገድ ስሄዱ መቆየታችው የሚታወቅ ሆኖ፣ ኣሁንም በስርአቱ  የረቀቁ የመቅጫ ህግ  ያለ ምንም ተቃውሞ ልማፅደቅ በዚህ ሳምንት ወደ ፓርላማ እንደሚያቅርቦው ሲገለፅ፣ የተቃውሞ መልእክት  በኮምፒተር ለማስተላለፍ ይችላሉ ላልዋቸው ወገኖች ለዚህ ኣዋጅ ተገን በማድረግ በብዛት ለመያዝና ለመቅጣት  ያለመ እንደሆነ  ለማወቅ ተቻለ።
   በተጨማሪም  በኮምፒተር ወንጀል  እየታየ ነው በሚል ሰንካላ ምክንያት፣  ረቂቅ ኣዋጁ  መውጣቱ  የኢህአዴግ አዋጅ ህግ  የገዥው ስርአት ሌላ ዘገባ እንደሆነ፣ በተለይ ደግሞ ወታደራዊ መረጃ የሚገኝባቸው የኮምፒተሮች ፋይሎችን ኣንዳይጠፉና እንዳይሰረቁ ልዩ  ትኩረት ሊያደርግ ነው የተባለ መሆኑንና፣ ለኢህአዴግ  ከስልጣኑ ሊያስወግዱት ይችላሉ የሚባሉት ቡድኖችና  ግለ ሰዎችም  ትኩረት በማደረግ፣ ለመቆጣጠር  ያለመ ሁኖው፣  በኮምፒተር  ወንጀል ለተከሰሰ ሰው ደግሞ  ከ15 እስከ 25 ኣመት በፁኑ መታሰር እንደሚጠብቅበት የውጣው ረቂቅ ህጉ ድግሞ ታውጆ እንደሚወጣ እየተገለፀ ነው።
 

No comments:

Post a Comment