Saturday, July 23, 2016

ሰሞኑን በርካታ ወጣቶች የወያኔ ኢህአዴግን ብልሹ አስተዳደር በመቃወም ወደ ትግራይ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ ትህዴን ማሰልጠኛ ማዕከል ተቀላቀሉ።



በዚህ ሳምንት የወያኔ ኢህአዴግን የተበላሸ አስተዳደር በመቃውም ወደ ትህዴን ማሰልጠኛ ማዕከል ከተቀላቀሉት መካከል ለመጥቀስ፦
1.ገዛኢ ኃይሌ ከሰሜን ምዕራብ ትግራይ ዞን፣ ታህታይ አድያቦ ወረዳ፣ ሰንትርለይ ቀበሌ
2.ጌትነት ፀጋይ ከሰሜን ምዕራብ ትግራይ ዞን፣ ታህታይ አድያቦ፣ ወረዳ ዓዲ ሐገራይ ቀበሌ
3.ኤልያስ አለምሰገድ ከሰሜናዊ ምዕራብ ዞን፣ ታህታይ ቆራሮ ወረዳ በለስ ቀበሌ
4.ሻንበል ተስፋሚካኤል ከማዕከላዊ ዞን፣ መረብ ለኽ ወረዳ፣ አዲ ጋባት ቀበሌ
5.ሐብቶም ብርሃኔ ከሰሜን ምዕራብ ዞን፣ ታህታይ አድያቦ ወረዳ፣ ዓዲ አውኣላ ቀበሌ
6.ገብረትንሳኤ ሐድሽ ከማዕከላዊ ዞን፣ መረብ ለኸ ወረዳ፣ ምህቋን ቀበሌ፣ መንደር ስፍራ ጨው
7.ስዩም አብርሃ ከሰሜናዊ ምዕራብ ዞን፣ ሰለኽለኻ ወረዳ፣ ምንጥል ቀበሌ
8.ብርሃኔ አባዲ ከማዕከላዊ ዞን፣ መረብ ለከ ወረዳ፣ ጠራውር ቀበሌ
9.ተኽለ ተስፋ ገብሩ ከማዕከላዊ ዞን፣ አህፈሮም ወረዳ፣ ዝባን ጉይላ ቀበሌ
10.ደሳለኝ መሐሪ ከምስራቅ ትግራይ ዞን፣ ጉሎማክዳ ወረዳ፣ ዛላምበሳ ቀበሌ 
11.አማኑኤል ተስፋይ ከምስራቅ ትግራይ ዞን፣ ኢሮብ ወረዳ፣ አለቲና ቀበሌ
12.ገብረ ተስፋ ከማዕከላዊ ዞን፣ መረብ ለኸ ወረዳ፣ ጠራውር ቀበሌ
13.ፊልሞን ክፍሌ ከምስራቅ ትግራይ ዞን፣ ጉሎማክዳ ወረዳ፣ ዛላምበሳ ቀበሌ 
14.ጎይትኦም ብርሃኔ ከማዕከላዊ ዞን፣ አሕፈሮም ወረዳ፣ ሆያ ቀበሌ
15.ሐጎስ ገብረ ከምስራቅ ትግራይ ዞን፣ ኢሮብ ወረዳ፣ አለቲና ቀበሌ 
16.ሚኪኤለ ሐዱሽ ከምስራቅ ትግራይ ዞን፣ ጉሎማክዳ ወረዳ፣ ዛላምበሳ ቀበሌ 
17.ወላይ በርሄ ከሰሜናዊ ምዕራብ ዞን፣ ላዕላይ አድያቦ ወረዳ፣ ዓዲ ነብሪ ኢድ ቀበሌ ፣ሲሆኑ ወደ ትህዴን መምጫቸውን ምክንያት ሲገልፁ ፣ወጣቶች ሆነን ሰርተን እንዳንበላ ስራ የለም፣ዝም እንዳንል ደግሞ ሳንበላ እንዴት መኖር እንችላለን ካሉ በኋላ፣ በአሁኑ ጊዜ የአገራችን ወጣት ከቦታ ቦታ ተንቀሳቅሶ ሰርቶ እንዳይበላና እንዳይንቀሳቀስ በኢህአዴግ ስርዓት የፅጥታ ሃይሎች ፀጉረ ልውጥ እየተባለ ብዙ እንግልት እየደረሰበት ስላለ ፣እኛ ደግሞ ወደ ትግራይ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ትህዴን) ድርጅት በመቀላቀል የትጥቅ ትግል መርጠናል ሲሉ ገልፀዋል።
   ወጣት ኤልያስ አለምሰገድ በበኩሉ እኔ ነጋዴ ነበርኩ፣ ሱቅ ነበረኝ ከአቅሜ በላይ ግብር ክፈል ስለተባልኩ፣ ይሄንን ከመጠን ያለፈ ግብር ለመክፈል ገንዘብ ስለሌለኝ የስርዓቱ ካድሬዎች ሱቄን አሸጉት በማለት የደረሰበትን ኢፍትሃዊ አሰራር ገልጿል።


No comments:

Post a Comment