Saturday, July 5, 2014

በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ አመታዊ ግምገማ በሚል ምክንያት በሃሰን ሽፋ በተመራው ስብሰባ ላይ የተገኙት የበላይ የፌደራል ፖሊስ አመራሮች መንግስት በሰላማዊ ህዝብ ላይ የሚወስደው እርምጃ ተገቢነት የሌለውና የተሳሳተ ነው ሲሉ መግለፃቸው የደረሰን መረጃ አመለከተ፣፣



በመረጃ መሰረት በመላው ያገራችን ክፍል ተሰማርተው የሚገኙት የፌደራል ፖሊስ የበላይ አዛዦች የተገኙበትና በአዲስ አበባ ላይ የተካሄደው ስብሰባ ፌደራል ፖሊስ በህዝብ ላይ እየወሰደው ያለ የሃይል እርምጃ ትክክል አይደለም፤ መንግስት በፊደራል ፖሊስ እንዲፈፀም ስያወርደው የነበረ ትእዛዝ እስካሁን ድረስ ተግባር ላይ እንዲውል ብናደርገውም ትክክል እንዳልሆነና ይህ ድርጊትም ከህዝብ አይን የተሰወረ ስላልሆነ ከተጠያቂነት እንደማናመልጥ፤ በዚህም ምክንያት መንግስት በዚህ ጉዳይ እየተከተለው ያለ አካሄድ መስተካከል ይገባዋል በማለት ጥብቅ ማሳሰብያ እንዳቀረቡ ለማወቅ ተችለዋል፣፣
      በማስከተል በስብሰባው ላይ የተገኙት የፌደራል ፖሊስ አዛዦች ካሁን በኋላ ሰላማዊው ህዝብ እንዲደብደብ፤ እንዲታሰርና ባላዩ ላይ በደል እንዲደርስበት መመርያ አንሰጥም፤ በደል እየደረሰው ያለው ህዝብ አንድ ቀን ይጠይቀናልና ከዚሁ የስርአቱ አፋኝና ፀረ ህዝብ ድርጊት መውጣት አለብን በማለት ተቃውሞ ማሰማታቸውና አንዳንድ የፖሊስ አባላትም ስብሰባውን ረግጠው መሄዳቸውን መረጃው አክሎ አስረድተዋል፣፣