Saturday, December 6, 2014

የህወሓት ባለስልጣኖች በሙዝየም ውስጥ ያሉ የሰማዕታት ስዕሎች የህይወት ታሪካቸው የት አለ የሚል በህዝብ ለቀረበላቸው ጥያቄ ተገቢውን መልስ መስጠት ስላልቻሉ ይህንን ለመሸፈን ደግሞ በመደራበሽ ላይ ተጠምደው እንደሚገኙ ምንጮቻችን አስታውቁ።



   እንደምንጮቻችን መረጃ የህወሃት ባለስልጣናት 40ኛ አመታቸውን  የካቲት 11 ላይ ለማክበር እየተዘጋጁ ባሉበት ሰዓት በሙዚየሙ ውስጥ ያለው የተሰው ታጋዮች ስዕል ማንነታቸው ስለማይታወቅ፤ የነዚህ ሰዎች ስምና የታሪክ ማህደራቸው የት አለ? በማለት ህብረተሰቡ በሚጠይቅበት ሰዓት አንዳንድ የህወሃት አመራሮችና ካድሬዎችም ህዝቡ እያነሳው ካለው ጥያቄ ጋር በመስማማት በህወሃት የተሰውትን የታሪክና የሰነድ አያያዝ እየጠየቁ መሆናቸውን ለማወቅ ትችሏል።
 ከዚህ በመነሳት ደግሞ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች፤ የሰራዊት ከፍተኛ አመራሮችንና ከዚህ በፊት ታጋይ ለነበሩ በአሁኑ ግዜ የዞን አስተዳዳሪ ሁነው ያሉት፥ ለህዝቡ እባካችሁ የያዛችሁትን ወይ ደግሞ ያገኛችሁት የህወሃት  ዶክሜንት ካለ አሁን አስፈላጊ ሁኖ ስለተገኘ ተባበሩን እያሉ እየተየቁ መሆናቸውና የወረዳ አስተዳዳሪዎችና ህብረተሰቡ ግን አሁን አይደለም ታሪክ የሚጠየቀው!! እስካሁን የት ነበራችሁ? ለምን ቀድመውም በጥሩ ሁኔታ የማትሰንዱት እያሏቸው እንደሚገኙ ምንጮቻችን የላኩልን መረጃ አስታውቀ።