Saturday, April 25, 2015

ከሱዳን መንግስት ጋር በተፈጠረ ግጭት ምክንያት የአማራ ክልል ሰሜን ጎንደር ዞን የሆኑ የመተማና የቋራ የጠረፍ አካባቢ ትምህርት ቤቶች መዘጋታቸውን ምንጮቻችን ገለፁ፣



እንደምንጮቻችን ገለፃ መሰረት። ከዚህ በፊት በሱዳንና በኢትዮጵያ  ወታደሮች መካከል እየተፈጠረ በነበረ አለመግባባትና ግጭት ከሁለቱም ወገኖች በርካታ ህይወት እየጠፋ እንደነበር የገለፀው መረጃው። በአማራ ክልል ሰሜን ጎንደር ዞን የሆኑ የመተማ የቋራና ተመሳሳይ የጠረፍ አካባቢ ትምህርት ቤቶች መዘጋታቸውን አስረድተዋል፣  
   በአካባቢው ከባድ ውጥረት መንገሱን ተከትሎ የኢትዮጵያ መንግስት   ከሌሎች ግንባሮች የነበሩ የሰራዊት አባላትን ሚያዝያ 2 ቀን 2007 ዓ/ም  ለ2 ቀናት በባህርዳር መኮድ ማሰልጠኛ ማዕከል የምክር አገልግሎት እየተሰጡ ቆይተው በምሽት በጎንደር ዳንሻና ሁመራ ከተሞች መስፈራቸው ታውቋል፣