Wednesday, January 23, 2013

የሽረና ሑመራ ኗሪ ህዝብ የምርጫ ካርድ ባለመውሰድ በጸረ-ዴሞክራሲው የኢህአደግ መንግስት ላይ ያለውን ተቃውሞ በመግለጽ ላይ መሆኑ የደረሰን ዘገባ ያስረዳል፣




ጸረ-ዴሞክራሲው የኢህአደግ መንግስት ኢፍትሃዊ የዩስሙላ ምርጫ በማካሄድ የስልጣን እድሜውን ለማራዘም ሲል ህጻናትን “ለምርጫ ብልህ ሁን “ የሚል ጽሁፍ ያለበትን ቲ-ሽርት በማደልና እንዲለብሱት በማድረግ ህዝቡን ለመቀስቀስ የተለያዩ ሙከራዎችን በማድረግ ላይ ነው ፣
በተመሳሳይ አምባገነኑ የኢህአደግ ስርዓት የሸራሮ ከተማ ህዝብን እለታዊ ስራውን እንዳይሰራ በተለያዩ ስብሰባዎች ወጥሮ በመያዝና ከፍተኛ ጫና በማድረግ የምርጫ ካርድ እንዲወስድ በማስገደድ ላይ መሆኑ ከቦታው የደረሰን ዘገባ ያስረዳል፣
የፊታችን ሚያዝያ 2005 ዓ/ም ሊደረግ የታሰበው ምርጫ ካለፉት ምርጫዎች ሁሉ በከፋ መልኩ በህዝቡ ላይ ገና ከወዲሁ የተለያዩ ጫናዎች በማድረግ እንደተለመደው ህዝቡ ድምጹን ሰጥቶኛል ለማለት መንግስት በከፍተኛ ደረጃ እየተንቀሳቀሰ መሆኑ የደረሰን ዘገባ ጨምሮ ያስረዳል፣