Monday, January 21, 2013

በሽረ-እንዳስላሰ ከተማ እስር ቤት ከነበሩ እስረኞች መካከል ለስርዓቱ ስጋት ናቸው የተባሉት እስረኞች ወደ ደቡብ ትግራይ እዲዛወሩ ተደረገ።



እስረኞቹ በ ጥር 7 እና 8,2005 ዓ/ም በሁለት ስካንያ ተጭነው ከሽረ-እንዳስላሰ እስር ቤት በመውሰድ በደቡብ ትግራይ በሚገኘው ጣፌ በተባለ እስር ቤት እዲታሰሩ ተደርጓል ።
የእስረኞቹን ቦታ መቀየር ያስፈለገበት ዋና ምክንያት በሰሜን ምዕራብ ትግራይና በምዕራብ ትግራይ እየታየ ያለው ህዝባዊ ተቃውሞ በአምባገነኑ ስርዓት ላይ ስጋት ስለፈጠረ መሆኑ ከቦታው የደረሰን ዘገባ ያመለክታል።