በደረሰን ዘገባ መሰረት በከተማዋ 01 ቀበሌ የሚገኙ 68 መኖሪያ ቤቶች በሰኔ 7,2005 ዓ/ም በከተማዋ
በሚገኙ የጸረ-ዴሞክራሲው ስርዓት ባለስልጣናት ትእዛዝ ያለ ምንም ካሳና ተለዋጭ መሬት ቤታቸውን ያጡ በርካታ ዜጎች ወቅቱ የክረምት
ወራት ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ለዝናብ ፤ ጸሃይና ብርድ ተጋልጠው በችግር ላይ የገኛሉ።
በየጎዳናው ወድቀው ያሉት እመጫቶች ፤ ነብስ ጡሮች ፤ ህጻናትና ሽማግሌዎች የሚገኙባቸው በርካታ ዜጎች ለተለያዩ
በሽታዎች እየተጋለጡ ሲሆን ለሚመለከተው አካል በተደጋጋሚ ጥያቄ ቢያቀርቡም መፍትሄ እንዳልተሰጣቸው ለማወቅ ተችሏል።
ከጉንበት ወር 2005 ዓ/ም አጋማሽ ጀምሮ በዚች ከተማ በመንግስት ሃይሎች ቤታቸው የፈረሰባቸው በርካታ
ዜጎች በየጎዳናው ወድቀው ለተለያዩ በሽታዎች መጋለጣቸውን መዘገባችን የሚታወስ ነው።