Monday, April 7, 2014

በትግራይ ክልል ሰሜናዊ ምእራብ ዞን ፀለምቲ ወረዳ ውስጥ መጋቢት 16 2006ዓ/ም ለውሃ ጠለፋ ተብሎ የተመደበው ባጀት በስርአቱ አስተዳዳሪዎች እንደተጠፋፋ መንጮቻችን ከቦታው ገለፁ።



ይህ በአካባቢው ለሚሰራው ግድብ ተብሎ የተመደው ባጀት የወረዳው የውሃና መአድን ሃላፊ የሆነው አቶ ፍሰሃ ኪዳኑ የተባለው ባለ ስልጣንና ሌሎች በገንዘቡ ማጠፋፋት ተግባር ላይ የተሰማሩ ግብረአበሮቹ ከ 280 ሺ በር በላይ ለጥቅማቸው እንዳዋሉት ለማወቅ ተችለዋል።
     መረጃው በማስከተል ለግድቡ መስርያ ተብሎ በየግዜው ሲገዙ የቆዩ በርከት ያሉ ንብረቶች ከላይ የተጠቀሰው ባለስልጣንና ተባባሪዎቹ በሌሊት ጨለማን ተገን አድርገው በመሸጥ በርከት ያለ የህዝብና የሃገር ገንዘብ እንዳጠፋፉ መረጃው አክሎ አስረድተዋል።