Wednesday, April 23, 2014

በመቀሌ ከተማ የሚገኙ የፋይናንስ ሃላፊዎች ከስራ ባልደረቦቻቸው ጋር በመመሳጠር 1.7 ሚልዮን ብር እንዳጠፋፉ ምንጮች ከቦታው ገለፁ።



በመረጃው መሰረት ገንዘቡን ያጠፋፉት የመቀሌ ከተማ ፋይናንስ ሃላፊዎች የካቲት 15/2006 ዓ/ም በህዝቡ ተከሰው ወደ ፍርድ ከቀርቡ በኃላ ከ 8 ወር እስከ አንድ አመት እንደተወሰነባቸውና እነዚህ የፋይናንስ ሰራነኞችና ተባባሪዎቻቸውም-
1     አቶ አስመላሽ መሓሪ የበላይ ሃላፊ
2     አቶ ጌታቸው ግርማይ
3     ወይዘሮ መድህን አማረ
4     አቶ አማንኤል ስራፍኤል
5     ወይዘሮ ለተብርሃን ገብረሂወትና
6     ወይዘሮ ሮማን ግደይ የተባሉ መሆናቸው መረጃው ገልፀዋል።
   ይህ በንዲህ እንዳለ በህዝቡ በኩል 1.7 ሚልዮን ብር የሚያህል የህዝብና የሃገር ሃብት ሰርቀው ከ8 ወር እስከ 1 አመት እስራት መወሰኑና ፍርድ መሰጠቱ ሌሎች የመንግስት ሰራተኞ በስርቆት ስራ ላይ እንዲሰማሩ የሚያበረታታ ተግባር ነው ሲሉ የከተማው ነዋሪ ህዝብ ገልፀዋል።