Thursday, April 17, 2014

የኢ.ህ.አ.ዴግ ሰራዊት የበላይ መኮንኖች መሳርያዎች ሸጠው ላገኙት ገንዘብ በመከፋፈሉ ላይ ሳይስማሙ በመቅረታችው ምክንያት ራሳቸው እስከ መገዳደል ደረጃ መድረሳቸው ከሰራዊቱ ውስጥ ሸልኮ የደረሰን መረጃ ኣስታወቀ።



በመረጃው መሰረት በ31 ክፍለጦር የስለያ ሃላፊ የሆነው ሻምበል ካልአዩ ከነ ግብረአበሮቹ ጋር በማህበር ከሸጡት መሳርያና ጥይት የተገኘ 500 ሺ ብር ባከፋፈሉ ላይ በተፈጠረው አለመግባባት ድርሻውን ሳይሰጡት በመቅረታቸው ምክንያትና በኃላም በክፍለጠሩ በተደረገው ስብሰባ ላይ ሻምበል ካልአዩ በመሳርያዎች መሸጥ ተግባር ላይ እንደተሰማራ በመገምገሙ ምክንያት ክስብሰባው እንደወጣ በራሱ እጅ ሂወቱን ማጥፋቱን ለማወቅ ተችለዋል።
    በክፍለጦሩ ውስጥ እያጋጠመ ላለው ችግር እንዲፈታ ተብሎ የእዙ ባለ ስልጣን ሜ/ጄነራል ዮውሃንስ ወልደጀወርግስ ወደ ቦታው ደርሶ ሁኔታውን በማስመልከት ስብሰባ ቢያካሂድም በሰራዊቱ ውስጥ ለውጥ ማምጣት እንዳልተቻለና ይባሱን የከፋ አለመረጋጋት ሰፍኖ እንደሚገኝ የተገኘው መረጃ ኣስታውቀዋል።
     ይህ በንዲህ እንዳለ የ 22 ክፍለ ጦር ኣባል የሆነው አንድ ወታደር በተደጋጋሚ ከአመራሮቹ ይደርስበት በነበረው በደል ተማሮ መቶ አለቃ ደረጀ ካሳየ ለተባለው መኮነን መጋቢት 28/2006 ዓ/ም ብጥይት ተኩሶ እንደገደለው መረጃው አክሎ ኣስረድተዋል።