በትግራይ ሰ/ምዕራብ ዞን የሚገኘው የ 31ኛ ክ/ጦር ክበብ ገንዘብ ያዥ የነበረው ወ/ር ዋክኔ ባሳዝን ከአከባቢው
ሲሰወር ከ 200,000 ብር በላይ የክ/ጦሩ ክበብ ገንዘብ በእጁ እንደነበረ ለማወቅ ተችለዋል ፣
በአሁኑ ግዜ በሰራዊቱ ውስጥ በተንሰራፋው ብልሹ አስሰራር ፤ የኢህአደግ መንግስት እያጋጠመው ያለውን ህዝባዊ
ተቋውሞና ስርዓቱን በመጣል በሃገሪቱ መሰረታዊ ለውጥ ለማምጣት እየተካሄደ ያለውን የትጥቅ ትግል በመገንዘብ በርካታ የሰራዊቱ አባላት
አምባገነኑን ስርዓት እየከዱ ሲጠፉ ማየት የተለመደ ሆኗል ፣
ባለፈው ሳምንት የዜና ዘገባችን በሰራዊቱ ውስጥ በሚታየው አድልዎ የተሞላበት አሰራር ምክንያት በርካታ የስርዓቱ
ወታደሮች እርስበርሳቸው እንደሚገዳደሉና እራሳቸውንም የሚያጠፉ እንዳሉ መዘገባችን የሚታወስ ነው ፣