Tuesday, November 27, 2012

የኢህአደግ መንግስት በትግራይ ምዕራባዊ ዞን ያለውን ህዝባዊ ተቋውሞ ከወዲሁ ለመቆጣጠር አዳዲስ የስለላ ሰዎችን መድቦ መንቀሳቀስ መጀመሩን ከቦታው የደረሰን ዘገባ ያመለክታል ፣




በደርሰን ዘገባ መሰረት በዓዲ-ጎሹ ፤ በሑመራና በሌሎች አከባቢዎች እየታየ ያለውን ህዝባዊ ተቋውሞ በሃይል ለመጨፍለቅ ሲባል በርካታ አዳዲስ የደህንነት አባላትን ወደ አከባቢው በማሰማራት በሕብረተሰቡ ውስጥ እንዲበተኑ ተደርጓል ፣ እነዚህ አዳዲስ የስለላ ወኪሎች የሚመሩት በካልአዩና በሪሁን በተባሉ የድህንነት ሃላፊዎች አማካይነት መሆኑን ቷውቋል ፣
በአከባቢው የተመደቡት እነዚህ የድህነነት አባላትና ካድሬዎች በህዝብ ላይ ኢሰብአዊ ተግባራት መፈጸም በመጀመራቸው የአከባቢው ኗሪው ህዝብ ሁኔታውን በጥንቃቄ እየተከታተለው መሆኑ የደረሰን ዘገባ ጨምሮ ያስረዳል ፣