Saturday, January 11, 2014

በስሜናዊ ምእራብ ትግራይ ዞን የሚኖሩ ወገኖቻችን ማንነታቸው ባልታወቁ ሰዎች እየተገደሉ መሆናቸው ከቦታው ተገለጸ፣



በመረጃው መሰረት በታህታይ ቆራሮ ወረዳ ጣብያ በለስ ሲኖር የነበረ ኤፍሬም ገብረሂወት ኣለማዮህ የተባለ ንፁህ ወገን። በታህሳስ 20/2006 ኣ/ም ሽሬ ከተማ ውሎ ሲመለስና ቤቱ ኣካባቢ እንደደረሰ። ማንነታቸው ባልታወቁ ሰዎች ድምፅ ኣልባ በሆነ መሳርያ እንደተገደለና ገዳዮችም እንደተሰወሩ ለማውቅ ተችለዋል፣ 
 
     ይህ በንዲህ እንዳለ በተመሳሳይ መንገድ መደባይ ዛና ወረዳ ውስጥ በሰለክለካ ከተማም። እለታዊ ስራዋን በማከናወን ላይ ለነበረች ሊቺይ ደሳለኝ የተባለች ተማሪ። በታህሳስ 18/2006 ኣ/ም ለግዜው ስሙ ባልታወቀ ሰው እንደተገደለችና ገዳዩም በቦታው ሞቶ እንደተገኘ መረጃው ኣክሎ ኣስረድተዋል፣