Wednesday, October 22, 2014

በዚህ ሳምንት ለህወሃት ኢህአዴግ መንግስት በመቃወም በርከት ያሉ ወጣቶች ወደ ትግራይ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅንቄ ድርጅት ተቀላቀሉ፣


በሽረ ከተማ የሚገኘው ሆስፒታል ለህብረተሰቡ ተገቢውን አግልግሎት ሊሰጥ ባለመቻሉ ምክንያት የሰው ህይወት እየጠፋ እንደሚገኝ ምንጮቻችን አስታወቁ፣


በሁመራ ከተማ የሚገኙ የማዘጋጃ ቤት ሃላፊዎች መሬት ለድሃው ህብረተሰብ እየከለከሉ ቆይተው ከውጭ ሃገር ለመጡ ወዳጆቻቸውና ሃብታሞች እየሸጡላቸው እንደሚገኙ ምንጮቻችን ገለፁ፣



በትግራይ ማዕከላዊ ዞን የአክሱም ከተማ ነዋሪዎች ከውጭ ሃገር ለሚመጡ ዲያስፖራ ኢንቨስተሮች መቀበያ ገንዘብ እንዲያዋጡ በካድሬዎች እየተገደዱ እንዳሉ ምንጮቻችን አስታወቁ፣



በትግራይ ሰሜናዊ ምእራብ ዞን፤ ማይ ፀብሪ ከተማ የሚገኙ የህወሃት ኢህአዴግ ካድሬዎች የአካባቢውን ተማሪዎች በመሰብሰብ የህወሃት ሊግ አባላት እንዲሆኑ እያስገደዷቸው መሆናቸው ተገለፀ፣


በትግራይ ምእራባዊ ዞን፤ ቃፍታ ሁመራ ወረዳ፤ ማይ ካድራ ከተማ ውስጥ በስራ ላይ ተሰማርተው የሚገኙ ዜጎቻችን በስርአቱ ፖሊሶች ገንዘባችውን እየተነጠቁ መሆናቸውን ምንጮቻችን ከአካባቢው ገለፁ፣


በላዕላይ አድያቦ ወረዳ ህብረት በተባለው ቀበሌ የሚገኙ ሚልሻዎች ከዴምህት ጋር ትተባበራላችሁ ተብለው በፖሊሶች እየተያዙ በመታሰር ላይ እንደሚገኙ ምንጮቻችን ከቦታው ገለፁ፣



በትግራይ ምእራባዊ ዞን ሁመራ ከተማ የሚገኙ የህወሃት ኢህአዴግ ታጣቂዎች የግል ፍላጎታችሁን አናሟላም ላሉ ንፁሃን ወገኖች በመደብደብ እያሰቃዩዋቸው እንደሚገኙ ተገለፀ፣